==
| 2 ሰኑስረት | |
|---|---|
| የኻይከፐሬ ምስል | |
| የግብጽፈርዖን | |
| ግዛት | 1905-1888 ዓክልበ.? |
| ቀዳሚ | 2 አመነምሃት |
| ተከታይ | 3 ሰኑስረት |
| ሥርወ-መንግሥት | 12ኛው ሥርወ መንግሥት |
| አባት | 2 አመነምሃት |
==
ኻይከፐሬ፣ ፪ ሰኑስረትግብጽን በመካከለኛ መንግሥት (12ኛው ሥርወ መንግሥት) ከ1905 እስከ ምናልባት 1888 ዓክልበ. ግድም ድረስ የገዛፈርዖን ነበረ። የአባቱ2 አመነምሃት ተከታይ ነበር። በተለይ የሚታወቀው በኤል-ላሑን ስላሠራው ሀረም ነው።
በኑብካውሬ ፪ አመነምሃት ዘመነ መንግሥት በ፴፫ኛው ዓመት (1907 ዓክልበ. ግድም) ልጁን 2 ሰኑስረት ከእርሱ ጋር በጋርዮሽ ወደ ዙፋኑ አስነሣው። ከዚህ ሁለት ዓመት በኋላ በ1905 ዓክልበ. ግድም ኑብካውሬ ዓረፈና ፪ ሰኑስረት ለብቻው ፈርዖን ሆነ ይመስላል።
በጠቅላላ ስንት ዓመታት ያሕል እንደ ነገሠ ተከራካሪ ነው።ማኔጦን ለኻይከፐሬ ፪ ሰኑስረት እና ለተከታዩ3 ሰኑስረት ፈንታ ለሁለቱ አንድ ስም ብቻ አለው፤ እሱምሴሶስትሪስ ሲሆን ለ፵፰ ዓመታት እንደ ገዛ ይለናል። ይሄ ሴሶስትሪስ እስከእስኩቴስ ድረስ የዘመተ በአፈ ታሪክ ይባላል። ፫ ሰኑስረት ቢያንስ በከነዓን እንደ ዘመተ ይታወቃል፤ ለ፪ ሰኑስረት ግን ምንም ዘመቻ አይታወቅም።
የቶሪኖ ቀኖና የሚባለው የፈርዖኖች ዝርዝር ሰነድ ሁለቱንም ይለያል፤ ለ፪ ሰኑስረት ፲፱ ዓመታትና ለ3 ሰኑስረት ፴ አመታት ይሠጣል። ነገር ግን ለ፪ ሰኑስረት ከ፰ኛው ዓመቱ በላይ የሆነ ዓመት ቁጥር በሥነ ቅርስ ስለማይታወቅ፤ ብዙ መምህሮች ለ፰፣ ፱ ወይም ፲ ዓመታት ብቻ እንደ ነገሠ ያምናሉ።

መጀመርያ ፫ቱ ዓመቶቹ ከአባቱ ፪ አመነምሃት በጋርዮሽ ሲሆኑ፣ ከዚህ በላይ ልጁን 3 ሰኑስረት በጋርዮሽ ወደ ዙፋኑ እንዳስነሣው የሚመለከት ማስረጃ አለ። ከዚህ ውስጥ አንድ የፓፒሩስ ሰነድ ሁለቱን ፈርዖኖች ሲጠቅስ በ፪ ሰኑስረት ፲፱ኛው ዓመትና በ፫ ሱኑስረት ፩ኛው ዓመት እንዳለ ይታስብ ነበር። ሆኖም ሌሎች መምህሮች በተቃራኒው በ፫ሰኑስረት ፲፱ኛው ዓመትና በተከታዩ በ3 አመነምሃት 1ኛው ዓመት እንደሚለው ያምናሉ።
በዩጂን ሜሪል አስተሳሰብ፣ ይህ ፈርዖንዮሴፍን የሾመው በኦሪት ዘፍጥረት ፵፩ ዘንድ ይሆናል። ይህም ደግሞ በመጽሐፈ ኩፋሌ ካለው አቆጣጠር (2164 ዓ.ዓ. ወይም 1907 ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት ግድም) ጋር ይስማማል። በዚህ ሥርወ መንግሥት የሌሎቹ ፈርዖኖች ጠቅላይ ሚንስትሮች ሁሉ በስም ቢታወቁ፣ የዚህ ፪ ሰኑስረት ሚኒስትር ስም ግን ከቶ አልታተምም፤ በዘፍጥረትም የዮሴፍ ግብጽኛ ስም «ጸፍናት ፐዕናህ» ሆነ።
| ቀዳሚው 2 አመነምሃት | የግብፅ ፈርዖን | ተከታይ 3 ሰኑስረት |