አሪያኒስም ወይምየአሪያን ቤተ ክርስቲያን በአንድክርስቲያን ቄስአሪዩስ (250-328 ዓም) ትምህርቶች የተመሠረተ በሥላሴ የማያምንሀረ ጤቃዊ የተባለ እምነትና እንቅስቃሴ ነበር።
አሪዩስ እንዳስተማረኢየሱስ ክርስቶስ ወይም ወልድ ከእግዚአብሔር አብ በታች የተለየና የተፈጠረ አምላክ እንደ ነበር አለ፣ እንጂ ሥላሴን አላስተማረም። እግዚአብሔር ከዓለም በፊት ኢየሱስን ቢፈጥርም፣ ኢየሱስ ግን ያልኖረበት ጊዜ ነበር፤ ከአብ በታች የተለየ ንዑስ አምላክ ነው ብሎ ያስተምር ነበር።
አሪዩስ ካረፈ በኋላ አሪያኒስም ለጊዜው በምሥራቁየሮሜ መንግሥት እየተደገፈ እምነቱ ወደ አንዳንድ ጀርመናዊ ብሔር ተስፋፍቶ ነበር፤ ለጥቂት ዘመናት እስከ 663 ዓም ድረስ ቆየ። የ«አሪያኖች» ስም ከመሥራቹ አሪዩስ የተሰየመ ሲሆን፣ አሁን አንዳንድ ያልተማሩ ሰዎች «አርያኖች» ከሚለውሕንዳዊ-ኢራናዊ ስያሜ ጋራ ተስተዋቸዋል፤ በውኑ ግን «አሪያኖች» ከ«አርያኖች» ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም።