ቤኒን ወይም በይፋየቤኒን ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከምዕራብቶጎን፣ ከምሥራቅናይጄሪያን እና ከሰሜንቡርኪና ፋሶናኒጄርን ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋፖርቶ ኖቮ ሲሆን የመንግሥቷ መቀመጫ ግንኮቶኑ ከተማ ናት። የቤኒን የቆዳ ስፋት ወደ 110,000 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሆን የሕዝቧ ብዛት ደግሞ ወደ 9.05 ሚሊዮን ይገመታል።
የቤኒን ይፋ ቋንቋፈረንሳይኛ ሲሆን እንደፎንናዮሩባ የመሳሰሉት የሀገሪቷ ባህላዊ ቋንቋዎች ሰፊ ተናጋሪ አላቸው።የሮማ ካቶሊክ ክርስትና ብዙ ተከታዮች ሲኖሩት እስላሞች፣ ፕሮቴስታኖችና የቩዱ ተከታዮችም ይገኛሉ። ቤኒንየተባበሩት መንግሥታት፣የአፍሪካ ሕብረት እናም ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ናት።
ከ17ኛው እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን እ.ኤ.አ. የሀገሪቱ መሬት በዳሆሚ መንግሥት ነበር የሚመራው። በ17ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የአትላንቲክ የባሪያ ንግድ በአካባቢው ሰፍቶ ስለነበር ቦታው የባሪያ ጠረፍ ይባል ነበር። በ1892 እ.ኤ.አ. ፈረንሳይ አካባቢውን በመቆጣጠርየፈረንሳይ ዳሆሚ ብላ ሰየመችው። በ1960 እ.ኤ.አ. ዳሆሚ ነፃነቷን በማግኘት ለ፲፪ ዓመታት በዴሞክራሲያዊ መንግሥት ተመርታለች።
ከ1972 እስከ 1990 እ.ኤ.አ. ሀገሪቷ በማርክሲስት ሌኒኒስት አቋምየቤኒን ሕዝባዊ ሪፐብሊክ ተብላ ተሰመች። በዚህ ጊዜ በሀገሪቷ የኢኮኖሚ ውድቀት ተከስቶ ነበር። በ1991 እ.ኤ.አ. የቤኒን ሪፐብሊክ ተመሠረተ።
ቤኒን ወደ ውጭ የሚልከው ዋንኛ ምርትጥጥ ሲሆን ከዚህ በላይካሸው ለውዝ (Anacardium occidentale)፣ኮኮነት፣ዓሳ፣እንጨት ወደ ውጭ ይላካሉ።ፔትሮሊየምናወርቅም ይላካሉ። ባለፉት ዓመታት ውስጥ ቤኒን ለተግባራዊሳይንስ ምርመራ ጥናት አንጋፋ ማዕከል ሆናለች።
በደቡብ ቤኒን ባሕላዊ አበሳሰል፣ በተለይ የበቆሎዳቦ በኦቾሎኒ ወጥ ወይም በቲማቲም ወጥ ይጠቀማል።አሳ እናዶሮ ከሁሉ ተራ ሥጋዎች ናቸው፣በሬ፣ፍየልናየጫካ አይጥ ደግሞ ይበላሉ። በስሜን ቤኒን ባሕላዊ አበሳሰል፣ በተለይኮቴሃሬ በበቆሎው ፈንታ ይጠቀማል። ቤሬ ወይምአሳማ በጥብስ ወይም በወጣወጥ፣ፎርማጆ፣ኩስኩስ፣ሩዝ፣ባቄላ፣ፍራፍሬ በሰፊው ይጠቀማሉ።
እግር ኳስ ከሁሉ የሚወድ እስፖርት ሲሆን፣ በቅርብ ጊዜ ውስጥቤስቦል ወደ ቤኒን ገብቷል።